Crediti

PERFORMING ARTISTS
Emahoy Tsegué-Maryam Guèbrou
Emahoy Tsegué-Maryam Guèbrou
Performer
COMPOSITION & LYRICS
Emahoy Tsegué-Maryam Guèbrou
Emahoy Tsegué-Maryam Guèbrou
Composer

Testi

ያለሽበት ሀገር ፀሀይ ነው ደመና
እኔስ መጥቻለሁ ባንችም አልፀና
አባይን ተሻግሮ አለወይ ሰማይ
ሀገርስ አለወይ ኢትዮጵያውያን መሳይ
ከደመና በላይ አሻግሬ ባይ
አልታየኝ አለ ያገሬ ሰማይ
አልታየኝ አለ ያገሬ ሰማይ
እናቴን መተኪያ አጥቻለሁ እኔ
አንተ ያገሬ ውሃ አረንጓዴ አትልበስ
እጠጣሀለሁኝ አቋርጨ ስመለስ
አንተ ያገሬ ውሃ የጠረፍ ፏፏቴ
እየራከኝ አትሂድ አይችልም አንጀቴ
የመውደድ መናፈቅ አይንሽን ጨርሽ
ውሀ ተሸክሞ ታገኝዋለሽ
ውሀ ተሸክሞ ታገኝዋለሽ
ሀገሬ፣ ሀገሬ
ሀገሬ፣ ሀገሬ
አይልም ወይ ሰው
ክፋ ሲናገሩት ሆድ እየባሰው
መንገድ አጣሁ ብየ አገርሽን ጠይቄ
እስከመቼ ድረስ ባንቺ ተጨንቄ
እስከመቼ ድረስ ባንቺ ተጨንቄ
ሀገሬ፣ ሀገሬ
ሀገሬ፣ ሀገሬ
አይልም ወይ ሰው
ክፋ ሲናገሩት ሆድ እየባሰው
አንተ ያገሬ ውሃ አረንጓዴ አትልበስ
እጠጣሀለሁኝ ወዳባቴ ስመለስ
እጠጣሀለሁኝ ወዳባቴ ስመለስ
ሀገሬ፣ ሀገሬ
ሀገሬ፣ ሀገሬ
አይልም ወይ ሰው
ክፋ ሲናገሩት ሆድ እየባሰው
አንተ ያገሬ ውሃ የተሻገርኸው
አታሻግርም ወይ የናፈቀን ሰው
አታሻግርም ወይ የናፈቀን ሰው
ሀገሬ፣ ሀገሬ
ሀገሬ፣ ሀገሬ
አይልም ወይ ሰው
ክፋ ሲናገሩት ሆድ እየባሰው
ትመጫለሽ ብየ አገርሽን ጠይቄ
እስከመቼ ድረስ ባንቺ ተጨንቄ
እስከመቼ ድረስ ባንቺ ተጨንቄ
Written by: Emahoy Tsegué-Maryam Guèbrou
instagramSharePathic_arrow_out

Loading...