Lyrics

የዉበቷ ግርማ ከሩቅ የሚስበው ዳሌ ተረከዟ ሽንጧ የረቀቀው አይኗ እንደጦረኛ የሚያስበረግገው ደረቷ እንደጋሻ ደርሶ ሰፋ ያለው ጡቷ እንደአራስ ነብር አትንኩኝ የሚለው አንገቷ እንደሰጎን ተመዞ የወጣው አፏ እንደህጻን ልጅ የሚርበተበተው እንደቀትር እባብ ፍቅሯ የልቤን አዳራሽ እልፍኟ ታድርገው ካንጀቴ ውስጥ ገብታ ልቤን አንድ ለአንድ መታገል ሲያቅተው ሰው ሁሉ አንቺ ሰው በሰው ላይ ትጥያለሽ አሉ ኦይ ሰውነቷ እንደው ሰውነቷ አንቺ ካለሽበት ከቆምሽበት ምድር አንቺ ካለሽበት ከቆምሽበት ምድር መነኩሴው ከገዳም ጎሽ ይወጣል ከዱር አንበሳን በጡቻ እለው የነበረ ዝሆንን በጡቻ እለው የነበረ ነብርን በጡቻ እለው የነበረ እባብ ጭንቅላቱን እለው የነበረ ምነው ካንቺ ሲደርስ ልቤ ደነበረ ኣይ ሰውነትሽ እንዲያው ሰውነቷ ምነው እኔ ምነው እኔ (×3) ቻዪኝ እንዳመሌ ሰውነቷ እንዲያው ሰውነቷ (×3) አንጀቴና ሆዴ ተጣልተውብኝ አንተም አንተም ተው ብዬ እንዳልለው አንጀቴም አንጀቴ ሆዴም ሆዴ ነው ለማን እፈርዳለው ፍርድ አያውቅም ሰው ኦይ ሰውነቷ እንዲያው ሰውነቷ አንቺ አኩራፊ ሆነሽ እኔ ሆደ ባሻ አንቺ አኩራፊ ሆነሽ እኔ ሆደ ባሻ በቃ ተለያየን እስከመጨረሻ አበባው ፈነዳ ቡቃያው ደረሰ ፍቅሬ. ... ምነው ደፈረሰ ኣይ ሰውነቷ እንዲያው ሰውነቷ የኔና ያንቺ ብቻ ፍቅራችን ከሰመ የመለየት ጉጉት በኛ ላይ ዘመመ የመለየት ጉጉት በኛ ላይ ዘመመ ኦይ ሰውነቷ እንዲያው ሰውነቷ ሰውነቷ ሰውነቷ እንዲያው ሰውነቷ ኦይ ሰውነቷ እንዲያው ሰውነቷ ምነው እኔ ምነው እኔ ምነው እኔ ቻዪኝ እንዳመሌ ምነው እኔ ምነው እኔ ምነው እኔ ቻዪኝ እንዳመሌ
Writer(s): Traditional Lyrics powered by www.musixmatch.com
instagramSharePathic_arrow_out