Lyrics

መጠሪያ አልተገኘም የሚሆንሽ ላንቺ ተስማምቶ ቁንጅና እራሱ ነሽ ውበት ነፍስ ህይወትን ዘርቶ መጠሪያ አልተገኘም የሚሆንሽ ላንቺ ተስማምቶ ቁንጅና እራሱ ነሽ ውበት ነፍስ ህይወትን ዘርቶ አለተፈጠረም ሰው የለሽም አምሳያ የቁንጅና ጣርያ የውበት ማሰሪያ በሰፈሩ ሁሉ የሚያማምር ሞልቶ ውበትሽ እንደ አርማ የሚታየው ጎልቶ የንግስት ግርማ አለሽ አንገት የሚያስደፋ ቃልሽ ምስክር ነው እውነት እንዳልጠፋ ቢፈጠር ርቀት ከሰማይ ሰማይ እመጣ ነበር አይንሽን እንዳይ መጠሪያ አልተገኘም የሚሆንሽ ላንቺ ተስማምቶ ቁንጅና እራሱ ነሽ ውበት ነፍስ ህይወትን ዘርቶ መጠሪያ አልተገኘም የሚሆንሽ ላንቺ ተስማምቶ ቁንጅና እራሱ ነሽ ውበት ነፍስ ህይወትን ዘርቶ ዝልፍልፍ ነው ፀጉርሽ እንዳሻው ተኝቷል ወገብሽን እንዳላይ ደብቆ ይዞታል ዳሌሽም ተስማምቶ በምቾት ተቀምጧል ሽንጥሽ ለእጄት ያክል ለመያዣ ቀርቷል ጨረቃም አትውጣ ፀሀይም ትጥለቅ ጥርስሽ ላገር በቂ የሚያንፀባርቅ ኮኮቦች በላይሽ ከበው ያወራሉ ውበትሽ ማርኳቸው ዙርያሽን ያያሉ ጌጣጌጥሽን ጣይው ኩሉስ ለምንሽ እንከን ሳይወጣለት ተፈጥሮ ገላሽ መቀነትሽን ፍቺው ምን አንጀት አለሽ እባብ እና ነበር ቀንተው እያዩሽ አይንሽም ቅዱስ ነው ክፋት እንዳያይ ተረከዝሽ እንቡጥ ችሎ አቆመሽ ወይ ጠረንሽ የአበባ ንብን ያሳስታል ውበትሽ ለግላጋ ሰውን ያስገምታል
Writer(s): Samuel Alemu, Dawit Mellesse Lyrics powered by www.musixmatch.com
instagramSharePathic_arrow_out